በምሥራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በማፋክቸሪንግ ዲፓርትመንት በእንጨት ስራ ክፍል የተሰሩ የስብሰባ ጠረጴዛ ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ለክብርት አዳነች አቤቤ ርክክብ ተደረገ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ለወረዳ እና ለክፍለ ከተማ የቢሮ እና ለስብሰባ አገልግሎት የሚውሉ ጠረጴዛዎች በምሥራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በእንጨት ስራ ክፍል አሰልጣኞች ተሰርተው ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ለክብርት አዳነች አቤቤ ርክክብ ተደረገ፡፡ የቢሮ መገልገያ ቁሳቁሶቹ በሀገራችን ምርት የመጠቀም ልምድን ለማዳበር የውጪ ምንዛሪን ለማስቀረት ታስቦ የተሰሩ ናቸው፡፡